ዜና | Oduu | News
ቆሻሻን በተገቢው መንገድ በማስወገድ ምቹ የመኖሪያ አካባቢ እንዲፈጠር እየሰራ መሆኑን የልደታ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ገለጸ።

ጽ/ቤቱ ከተማ አቀፍ በማሆበረሰቡ የደረቅ ቆሻሻ ከምንጩ የመለየት ንቅናቄ ማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ የጽዳት አምባሳደሮች፣ባለሙያዎች፣የሽርክና ማህበራት፣ ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየ ዓለም እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝን በማስተካከልና ከምንጩ በመለየት በቅብብሎሽ በማጓጓዝ የሚፈለገው ቦታ በማድረስ አካባቢያችንን በንጽህና በመያዝ ለመኖሪያ ምቹ እንድትሆን በመተባበር ልንሰራ የሚገባ መሆኑን ገልጸዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሓዱሽ ሓጎስ በበኩላቸው የንቅናቄው ዓላማ ቆሻሻን በተገቢው መንገድ የሚበሰብሱ ቆሻሻዎችንና የማይበሰብሱትን ከምንጩ በመለየት ጥቅማ ላይ እንዲውል ለማድረግና ደረቅ ቆሻሻ ከሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ መልሶ ጥቅም ላይ እንዲዉሉ ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል። ደረቅ ቆሻሻን መልሶ ኡደት በማድረግ ይሰጠው ከነበረው አገልግሎት በሙሉ ወይም በከፊል ለሌላ አገልግሎት ማዋል በትኩረት ከተሰራበት የሀብት ምንጭ መሆኑን የገለጹት አቶ ኃዱሽ ደረቅ ቆሻሻን ጥቅም ላይ ለማዋል በሚከናወነው ተግባር የተደራጁ የሽርክና ማህበራት፣ባለሙያዎች፣የጽዳት አምባሳደሮችና ህብረተሰቡ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ደረቅ ቆሻሻን ከምንጩ በመለየት መልሶ የመጠቀም ባህልን ልናሳድግ ይገባል ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት አዲስ አበባ ከተማን ገጽታ የቀየሩ በርካታ የልማት ስራዎች መሠራታቸውን ገልጸው ቆሻሻን በየቦታው ከመጣል ተቆጥበን ቆሻሻን በአግባቡ በመለየትና መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል አካባቢያችን ለመኖሪያ ምቹ የተጀመሩ የልማት ስራዎችም ቀጣይ እንዲሆኑ መስራት የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የፅዳት ዘመቻውን የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤትና ከወጣት ማህበር ጋር በመተባበር ነው ያካሄዱት።

በልደታ ክ/ከተማ የፅዳት ዘመቻ ተከናወነ የዘመቻው ዓላማ ውብ ፅዱና አረንጓዴ አካባቢን በመፍጠር ሂደት ወጣቶች ሚናቸውን እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑን ተገልጿል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ሙስናን እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቅንጅት መታገል እንደሚገባ ተገለፀ።

ስልጠናውን የክፍለ ከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ከክ/ከተማ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና መከታተያ ክፍል ጋር በመተባበር ተሰጥቷል በመድረኩ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የጽዳት አምባሳደር ታዋቂ አርቲስቶች እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተገኝተዋል ተካፍለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ያየህ አለም እንዳሉት የሥነ ምግባር ጉድለትና ሙስናና ብልሹ አሰራር የሚፀየፍና የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጋ ለመፍጠር በሚደረገው የፀረ ሙስና ትግል ላይ የራሱን ሀላፊነት በመወጣት እንዳለበት ገልፀዋል የስልጠና ተሳታፊዎችም ስልጠናው የተሻለ መሆኑን በመግለፅ በሚደረገው የፀረ ሙስና ትግል ላይ ሁሉም የራሱን ሀላፊነት መወጣት አለበት በማለት አንስተዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና የመልካም አስተዳደርና ቅሬታ አፈታትን አፈፃፀም ገመገመ።

የልደታ የልደታ ክፍለ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ቤት የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸምን ከወረዳ አመራሮች ቡድን መሪዋችና ባለሞያዋች ጋር ገምግሟል። በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራት በቅንጅት የተሰሩና ጥሩ ውጤት የተመዘገበባቸው ናቸው ብለው ይህ ተግባር እንዲሳካም ሲሰሩ ለነበሩ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል። የክ/ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ ዓለም በክፍለ ከተማዉ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት እየተሰሩ ያሉ ስራዋች አበረታችና ችግር ፈቺ መሆናቸዉን ገልፀዉ በቀጣይ ተጠናክረዉ መቀጠል እንዳለባቸዉ ገልፀዋል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ መቅደስ ያደታ በበኩላቸው የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም የተሻ እንደተፈፀመና በቀጣይ ግን አገልግሎት አሰጣጡን ለማለቅ እንዲቻል ተከታታይነት ያለዉ ስራ መሰራት እንዳለበት አስቀምጠዋል :: የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሩብ ዓመቱ ስኬታማ ስራ ተሰርቷል ያሉ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ "ሳምንታዊ "የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።

በዘመቻው የክ/ከተማው አፈ ጉባኤ አቶ ዘሪሁን ሺፈርዳ /የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ጢቂ ድሪባ ፣የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ተወካይ አቶ እንግዳው ጋዴ፣አርቲስቶች ፣የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈውበታል። የልደታ ክ/ከተማ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ዘሪሁን ሺፈርዳ በዘመቻው ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ፅዳት የአንድ ተቋም ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ህብረተሰብ ቅንጅታዊ ተግባር ነው ብለው ማህበረሰቡ ፅዳትን ባህሉ በማድረግ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ አዲስ አበባን መፍጠር ይኖርበታል ብለዋል። አቶ ዘሪሁን አክለውም ብሎክ ሲፀዳ በድምር ውጤት ወረዳ ይፀዳል፤ ወረዳ ሲፀዳ ክ/ከተማ ሁሉም ክ/ከተሞች ሲፀዱ ደግሞ ከተማችን ውብ ትሆናለች ብለዋል። የክ/ከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ ዓለም በበኩላቸው ሁላችንም ለአካባቢ ፅዳት ትኩረት በመስጠት ከተማችንን ውብና ማራኪ ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል። አካባቢያችንን ዘወትር በማፅዳት ውብ፣ ፅዱና ምቹ የሆነ የመኖሪያ አካባቢን መፍጠር ይኖርብናል ብለዋል። አቶ ያየህ አክለውም አዲስ አበባን እንደ ስሟ ንፁህና ፅዱ እናደርጋለን ለዚህም ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት፥ ህብረተሰቡ ዘውትር አከባቢውን ማፅዳትና ቆሻሻን በተገቢው ቦታ ማከማቸት እንደሚኖርበት ተናግረዋል #ፅዳት የዘመናዊነት መገለጫ ነው!! #ዘውትር አከባቢያችን በማፅዳት ፅዱ፣ ውብና ለመኖሪያ ምቹ የሆነ ስፍራን እንፍጠር!!

image
image
image
image