image
image
image
image
image

በክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ እንደሚገባ ተገለፀ!!

ህዳር 11, 2018
የጉለሌ ክፍለ ከተማ የሲቪክ ማህበራት በክረምት መሃግብር የተተከሉ ችግኞችን የውሃ ማጠጣት ፕሮግራም አከናወኑ :: በፕሮግራሙ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ምክትልና ፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት ዋቅጋሪ እንደገለፁት ከሆነ በክረምት መርሃግብር በርካታ ንቅናቄዎችን በመፍጠር በርካታ ችግኞች መተከላቸውን የገለፁ ሲሆን ፍሬ እስኪያፈሩ ድረስ ሁሉም ባለድርሻ አካል ተቋማት የሲቪክ ማህበራት ሊንከባከቧቸውና ሊጠብቋቸው እንደሚገባ ገልፀዋል:: የክፍለ ከተማው የብልጽግና የፓለቲካ ዘርፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሪክተር አቶ ደረጀ ክንፈ እንደገለፁት የሲቭክ ማህበራት ካላቸው ተልህኮ በተጨማሪ በዚህ የችግኝ እንክብካቤ ላይ መሳተፋቸውን አመስግነው እስከመጨረሻው የተክሎቹን እድገት እስክናረጋግጥ እንክብካቤያችንን ማስቀጠል ይኖርብናል በማለት ገልፀዋል::

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች