image
image
image
image
image

የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን በመቀነስ ለነዋሪዎቿ ምቹና ጤናማ ክ/ከተማን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ መሆኑን የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

ታህሳስ 16, 2018
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት በአየር ንብረት ለውጥ አያያዝ፣ በአካባቢ ብክለት መከላከልና በብዝሃ ሕይወት ዙሪያ በተመለከተ ለተለያዩ ለሲቪክ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በስልጠናው መድረክ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሩ መንግስቱ እንደገለጹት‎ ክፍለ ከተማችን ሰፊ የሆነ የተፈጥሮ ሃብት ክምችት ያላት በመሆኗ ይህንን ሀብት ለመጠበቅና በአግባቡ ለመጠቀም ሰፊ የሆነ አካላዊና ስነ-ሕይወታዊ ስራዎች በመስራት እንዲሁም ከተማችን ከተጋረጠባት ከፍተኛ የብክለት ችግር ለመታደግ የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት ብክለት የሚያደርሱ ተቋማት በመለየት ልማት እና አካባቢን ለማጣጣም አካባቢ ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ እንዲሰሩ የማድረግ እንዲሁም ሕብረተሰቡ ስለ አካባቢ ያለዉን ግንዛቤ በተለያየ መንገድ በማሳደግ እና ድጋፍ በማድረግ ለአካባቢ ተቆርቋሪ ሕብረተሰብ ለመፍጠር ጥረት ይደረጋል ብለዋል ፡፡ ‎ ‎በቀጣይም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የአከባቢ ብክለትን በመከላከል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን እና የአረንጓዴ ልማት ፕሮግራሞችን አጠናክሮ በመስራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት በጋራ መረባረብ እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡ ‎ ‎

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች