image
image
image
image
image

የጉለሌ ክ/ከተማ አስተዳደር ባለሙያዎችና አመራሮች በ2017/18 በክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን ውሃ የማጠጣት እና ሌቾች የእንክብካቤ ስራዎችን በዛሬው ዕለት አከናወኑ።

ታህሳስ 15, 2018
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በንግግራቸው እንደሀገር የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት የተስተካከለ የዝናብ ስርጭት እንዲኖር፣ ለኑሮ ተስማሚ የሆነ አካባቢ ለመፍጠር፣ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግና፣ የኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት ፋይዳው የጎላ በመሆኑ ችግኝ ተክሎ ማሳደግ የዘውትር ተግባራችን መሆን አለበት ሲሉ ተናግረዋል። የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው በበኩላቸው በችግኝ እንክብካቤ መርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የመተባበርና የአንድነት ውጤት ማሳያ መሆኑን ገልጸው የሚተከሉ ችግኞች የአየር ንብረት ለውጡን ከመከላከል ባሻገር ለከተማው ውበት የሚሰጡና ለምግብነት የሚውሉ በመሆናቸው መትከል ብቻውን ውጤት ባለመሆኑ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ የሁላችንም ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ብለዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች