image
image
image
image
image

የጉለሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ከUNDP ኦርጋናይዜሽንጋር በመተባበር በንብ ማነብ ሙያ ዘርፍ ያሰለጠናቸውን አባወራዎችና እማወራዎች አሰልጥኖ አስመረቀ።

ጥቅምት 14, 2018
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ከUNDP ኦርጋናይዜሽን ጋር በመተባበር ለአየር ንብረት ተጋላጭ ለሆኑ አካባቢዎች በክፍለ ከተማው ወረዳ 6 የእንጦጦ ደን አካባቢ ላይ የሚኖሩ በኑሮአቸው ሊደጎሙ ለሚገቡ የህብረተሰብ ክፍሎች 70 አማወራዎችና አባወራዎች በንብ ማነብ አሰልጥኖ አስመረቀ፡፡ በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የጉለሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሃና ምህረቱ እንደተናገሩት እንደ ክፍለ ከተማ ሰው ተኮር የሆኑ ስራዎችን በዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ሲሆን የዛሬው ምርቃት የደን አካባቢ ነዋሪዎች ገቢ መፍጠሪያ እንዲሆን በማድረግ የአካባቢውን ተፈጥሮ ሃብት ተንከባካቢ እንደሆኑ ገልጸው በንብ ማነብ ዘርፍ አሰልጥኖ ስራ ዕድል ዕድል እንዲያገኙ ተሰርቷል ህብረተሰቡ የሚኖርበትን አካባቢ የሚገኘውን የደን ስፍራ ከጎጂ ነገሮች በመጠበቅ የኑሮ ሁኔታዎችን በማሻሻል ጠንክሮ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስልጠና ክፍል ምክትል ኃላፊ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በበኩላቸው ሰልጣኞች በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ያገኙትን ስልጠና ወደ ተግባር መቀየርና ምርትና ምርታማነታቸውን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች