image
image
image
image
image

አከባቢያችንን ከብክለት ለመከላከል ሁሉም የማህብረሰብ ክፍል የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ታህሳስ 18, 2018
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አከባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት በአከባቢ ብክለት፣ በብዝሃ ህይወትና ስነምህዳር እና በአየር ንብረት ለውጥ ዙርያ ለትምህርት ተቋማት የአካባቢ እንክብካቤ ክበብ አባላት ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በስልጠናው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሀና ምህረቱ እንደተናገሩት በብዝሃ ህይወት ጥበቃ፣ለአከባቢ ብክለትን ተቆርቋሪነት ያለውን ግንዛቤ በማሳደግ በአከባቢ ላይ የሚደርሱ የአየር ብክለቶችን በመከላከል ንጹህና ጤናማ አካባቢ የመኖር መብትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊዎችም የተፈጠረላቸው ግንዛቤ መሰረት በማድረግ አከባቢያቸውን ከብክለት ለመጠበቅና ለመከላከል የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች