image
image
image
image
image

የአዲስ አበባ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ አዘጋጅነት በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከ6 ኪሎ ፣ በሽሮ ሜዳ ፣ እንጦጦ የለማው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ጉብኝት ተካሄደ።

ታህሳስ 17, 2018
በክፍለ ከተማው የለማው የኮሪደር ልማት ስራዎችን በጉብኝቱ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ስዩም ከበደ ፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ወገሴ፣ የጉለሌ ክ/ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው : የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ታደሰ ፣ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ወንዱ አሰፋ ፣ በየደረጃው የሚገኙ የዘርፉ አመራሮች ፣ የሀይማኖት አባቶች ፣ አባገዳዎች ፣ ሀደስንቂዎች ፣ በጎ የማህበረሰብ አንቂዎች፣ አርቲስቶች፣ ስፖርተኞች እና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ጎብኝተዋል። ለጎብኝዎች ገለጻ ያደረጉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት መንግስት በርካታ ሰው ተኮር የሆኑ ተግባራትን ፣ የማይደፈሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ፣ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን በማከናወን ከቁልቁለት ጉዞ አውጥቶ የማንሰራራት ጊዜያት ላይ ደርሰናል መጪዎች ጊዜያት የከፍታ ዘመን እንዲሆን ሁላችንም በተሰማራንበት ዘርፍ የላቀ ለውጥ የምንተጋበት መሆን ይገባል ብለዋል። የኮሪደር ልማቱ የአስፓልት መንገድ ዝርጋታ ፣የእግረኛ መንገድ ፣ የሳይክል መስመር ፣ የህጻናት መጫወቻ ቦታዎች ፣ የስፖርት ማዝወተሪያ ስፍራዎች ፣ የህዝብ መዝናኛ ፕላዛዎችና አረንጓዴ ፓርኮች ፣ መጸዳጃ ቤቶች ፣ የንግድ ሱቆች ፣ የመኪና ማቆሚያና ተርሚናሎች በውስጡ አካቷል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች